2A Lithos Rd, Hampstead, London NW3 6EF Phone postmaster@ethiopiancommunity.co.uk
Follow us:
ስለ እኛ

የኢትዮጵያውያን ተራድኦ ማህበር በብሪታንያ

የኢትዮጵያውያን፡ ተራድኦ፡ ማህበር፡ በብሪታንያ፡ እ፡ኤ፡አ፡ በ1983 ፡ በአንጋፋነት፡ ተቋቁሞ፡ ላለፉት፡ 36፡ አመታት፡ በተለያዩ፡ ጊዜያት፡ በተለያዩ፡ ምክንያቶች፡ ከውድ፡ አገራቸው፡ በስደት፡ ለወጡ፡ በብዙ ሺህ፡ ለሚቆጠሩ፡ ኢትዮጵያውያን፡ ብሄር፡ ቋንቋ፡ ሀይማኖትን፡ ጾታ፡ ሳይለይ፡ ከፖለቲካ,፡ ነጻና፡ ገለልተኛ፡ በመሆን፡ የተለያዩ፡ አገልግሎቶችን፡ ማለትም፣ የስደተኝነት፡ ማመልከቻ፡ ድጋፍ፣ የመኖሪያ፡ ቤት፡ ፍለጋ፣ የጤና፡ የሴቶች፣ የህጻናትና፡ የአዛውንቶች፡ አገልግሎት፣ እንግሊዝኛ፡ቋንቋ፡ ትምህርት፣ የስራ፡ ፍለጋ፡ ስልጠናና፡ ምክር፣ የመሳሰሉትን፡ ማህበራዊ፡ አገልግሎቶችንና፡ ድጋፍ፡ በመስጠት፡ ላይ፡ ይገኛል።

የተራድኦ፡ ማህበሩ፡ የተቋቋመው፡ በእንግሊዝ፡ አገር፡ የግብረ፡ ሰናይ፡ ድርጅቶች፡ ህግና፡ ድንጋጌ፡ በመሆኑ፡ ከፖለቲካ፡ ነጻና፡ ገለልተኛ፡ ሆኖ፡ ለህብረተሰቡ፡ ተገቢውን፡ አገልግሎት፡ እየሰጠ የገኛል።

ምንም፡ እንኳን፡ በአሁኑ፡ ወቅት፡ በከፍተኛ፡ የገንዘብ፡ እጥረት፡ ምክንያት፡ ሙሉ አገልግሎቶች፡ መስጠት፡ባይቻልም፡ የተራድኦ፡ማህበሩ፡ በወጣት፡ ኢትዮጵያውያን፡አመራር፡ በአዲስ መልክ፡ ተደራጅቶ፡ የተለያዩ፡ እቅዶች፡ በመንደፍ፡ የገንዘብ፡ አቅሙን፡ ለማጠናከርና፡ ኢትዮጵያውያንን፡ በሰፊው፡ ለማሳተፍ እና ለማገልገል፡ ተነሳስቷል።

በተጨማሪም፡የተራድኦ፡ ማህበሩ፡ አሁን፡ በኪራይ፡ የሚጠቀምበትን፡ ከፍተኛ፡ ህንጻ፡ በግዥ፡ መልክ፡ የራሱ፡ ንብረት፡ በማድረግ፡ "የኢትዮጵያውያን፡ የባህል፡ማእከል።" Ethiopian Centre" ለማቋቋም፡ የረጅም፡ጊዜ፡ እቅድ፡ ይዞ በምንቀሳቀስ ላይ ይገኙል።

የምንሰራው
እኛ ማን ነን

የግለሰብ አባላትን ልዩነት እና ራስን የማስተዳደር መብት እናከብራለን።

ተልዕኮ
የማህበረሰብ ደህንነት

ECB የአባላቱን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ትምህርታዊ፣ ጤና ነክ እና የማህበረሰብ ደህንነት ለማጎልበት ቁርጠኛ ነው፤ እንዲሁም በውጭ ሀገር የሚኖሩ የኢትዮጵያውያን ልጆች ቅርሳቸውን እንዲያደንቁ ለማስቻል የኢትዮጵያን ባህልና ወግ ለማስተዋወቅ እና ለመጠበቅ ይሰራል።

ራዕይ
ሕያው ማኅበረሰብ

አባላቱ በህብረተሰቡ ውስጥ ውጤታማ እና ብልጽግና የተጎናጸፉ የሆኑ፣ ሕያው እና ጠንካራ የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብን ይገንቡ።

መሠረታዊ እሴቶች
የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብ

ተጠያቂነት፣ ግልጽነት፣ ሁሉን አቀፍነት እና ርህራሄ። በብሪታንያ ለሚገኙ ሁሉም ሰዎች አስተማማኝ፣ ጥራት ያለው እና ተደራሽ የሆነ የማህበረሰብ አገልግሎት ማቅረብ።

What We Do

ስለ ሥራችን የበለጠ ይወቁ እና ይሳተፉ

የባህል ፕሮግራሞች

የኢትዮጵያ ቀን በዓል አከባበር። ስፖርት። ከትምህርት ሰዓት ውጪ እና የበጋ የወጣቶች ፕሮግራሞች።

የማህበረሰብ ተደራሽነት

የጤና ትምህርት። የጥብቅና ሥራ። የዜጎች ተሳትፎ።

የሥራ መስክ ትውውቅና ግንኙነት

የግብዓት ማዕከል፤ እንግሊዝኛ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ።

ያግኙን

ጥያቄዎች አሉዎት ወይስ መሳተፍ ይፈልጋሉ?

በኢሜይል ወይም በስልክ ያግኙን።

ለህብረተሰባችን በፍቅር ተነሳሳ። የተለያዩ አገልግሎቶችን እናቀርባለን መጥተው ይጎብኙን ወይም ይደውሉልን ወይምWhatsApp.