የኢትዮጵያውያን፡ ተራድኦ፡ ማህበር፡ በብሪታንያ፡ እ፡ኤ፡አ፡ በ1983 ፡ በአንጋፋነት፡ ተቋቁሞ፡ ላለፉት፡ 36፡ አመታት፡ በተለያዩ፡ ጊዜያት፡ በተለያዩ፡ ምክንያቶች፡ ከውድ፡ አገራቸው፡ በስደት፡ ለወጡ፡ በብዙ ሺህ፡ ለሚቆጠሩ፡ ኢትዮጵያውያን፡ ብሄር፡ ቋንቋ፡ ሀይማኖትን፡ ጾታ፡ ሳይለይ፡ ከፖለቲካ,፡ ነጻና፡ ገለልተኛ፡ በመሆን፡ የተለያዩ፡ አገልግሎቶችን፡ ማለትም፣ የስደተኝነት፡ ማመልከቻ፡ ድጋፍ፣ የመኖሪያ፡ ቤት፡ ፍለጋ፣ የጤና፡ የሴቶች፣ የህጻናትና፡ የአዛውንቶች፡ አገልግሎት፣ እንግሊዝኛ፡ቋንቋ፡ ትምህርት፣ የስራ፡ ፍለጋ፡ ስልጠናና፡ ምክር፣ የመሳሰሉትን፡ ማህበራዊ፡ አገልግሎቶችንና፡ ድጋፍ፡ በመስጠት፡ ላይ፡ ይገኛል።
የተራድኦ፡ ማህበሩ፡ የተቋቋመው፡ በእንግሊዝ፡ አገር፡ የግብረ፡ ሰናይ፡ ድርጅቶች፡ ህግና፡ ድንጋጌ፡ በመሆኑ፡ ከፖለቲካ፡ ነጻና፡ ገለልተኛ፡ ሆኖ፡ ለህብረተሰቡ፡ ተገቢውን፡ አገልግሎት፡ እየሰጠ የገኛል።
ምንም፡ እንኳን፡ በአሁኑ፡ ወቅት፡ በከፍተኛ፡ የገንዘብ፡ እጥረት፡ ምክንያት፡ ሙሉ አገልግሎቶች፡ መስጠት፡ባይቻልም፡ የተራድኦ፡ማህበሩ፡ በወጣት፡ ኢትዮጵያውያን፡አመራር፡ በአዲስ መልክ፡ ተደራጅቶ፡ የተለያዩ፡ እቅዶች፡ በመንደፍ፡ የገንዘብ፡ አቅሙን፡ ለማጠናከርና፡ ኢትዮጵያውያንን፡ በሰፊው፡ ለማሳተፍ እና ለማገልገል፡ ተነሳስቷል።
በተጨማሪም፡የተራድኦ፡ ማህበሩ፡ አሁን፡ በኪራይ፡ የሚጠቀምበትን፡ ከፍተኛ፡ ህንጻ፡ በግዥ፡ መልክ፡ የራሱ፡ ንብረት፡ በማድረግ፡ "የኢትዮጵያውያን፡ የባህል፡ማእከል።" Ethiopian Centre" ለማቋቋም፡ የረጅም፡ጊዜ፡ እቅድ፡ ይዞ በምንቀሳቀስ ላይ ይገኙል።
የምንሰራውECB የአባላቱን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ትምህርታዊ፣ ጤና ነክ እና የማህበረሰብ ደህንነት ለማጎልበት ቁርጠኛ ነው፤ እንዲሁም በውጭ ሀገር የሚኖሩ የኢትዮጵያውያን ልጆች ቅርሳቸውን እንዲያደንቁ ለማስቻል የኢትዮጵያን ባህልና ወግ ለማስተዋወቅ እና ለመጠበቅ ይሰራል።
አባላቱ በህብረተሰቡ ውስጥ ውጤታማ እና ብልጽግና የተጎናጸፉ የሆኑ፣ ሕያው እና ጠንካራ የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብን ይገንቡ።
ተጠያቂነት፣ ግልጽነት፣ ሁሉን አቀፍነት እና ርህራሄ። በብሪታንያ ለሚገኙ ሁሉም ሰዎች አስተማማኝ፣ ጥራት ያለው እና ተደራሽ የሆነ የማህበረሰብ አገልግሎት ማቅረብ።
የኢትዮጵያ ቀን በዓል አከባበር። ስፖርት። ከትምህርት ሰዓት ውጪ እና የበጋ የወጣቶች ፕሮግራሞች።
የጤና ትምህርት። የጥብቅና ሥራ። የዜጎች ተሳትፎ።
የግብዓት ማዕከል፤ እንግሊዝኛ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ።
ለህብረተሰባችን በፍቅር ተነሳሳ። የተለያዩ አገልግሎቶችን እናቀርባለን መጥተው ይጎብኙን ወይም ይደውሉልን ወይምWhatsApp.